አሜሪካ በፈጸመቸቻው ጥቃቶች 53 ኢራናውያን መገደላቸውን የአገሪቱ ባለሥልጣን አስታወቁ

የፎቶው ባለመብት, Tasnim
አሜሪካ በኢራን ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት መልሳ በመጀመር 11ኛ ቀኑን በያዛበት በአሁኑ ጊዜ ኢራን ውስጥ 53 ሰዎች መገደላቸውን የአገሪቱ የጤና ሚኒስትር አስታወቁ።
የጤና ሚኒስትሩ ሆሴይን ኬርማንፑር የአሜሪካ ጥቃት በአገራቸው ዜጎች ላይ ያደረሰውን ጉዳት በተመለከተ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ላይ አስፍረዋል።
ሚኒስትሩ ተገደሉ ካሏቸው ሰዎች በተጨማሪ 592 ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ያመለከቱ ሲሆን፣ ነገር ግን በጥቃቶቹ የተገደሉት እና ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወታደሮች ወይም ሲቪሎች መሆናቸውን አልጠቀሱም።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ባለፈው የካቲት ወር አሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን ጋር ጦርነት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ ቢያንስ 18 የአሜሪካ ወታደራዊ ወታደሮች ተገድለዋል።
ከቀናት በፊት የአሜሪካንን ጥቃት ተከትሎ ኢራን በዮርዳኖስ በሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ የሚሳዔል ጥቃት መፈጸሟን አሜሪካ አረጋግጣለች። ሞዋፍቃት አል-ሱልቲ በተባለው ጦር ሰፈር ላይ በተፈጸመው በዚህ ጥቃትም ሦስት ወታደሮቿ ተገድለውባታል።
አራተኛው ወታደሯ ደግሞ ኢራቅ ኤርቢል ውስጥ አንድ ጥቃት ፈጻሚ የኢራን ድሮን እንዲፈነዳ በተደረገበት ጊዜ ሕይወቱ ማለፉ ተገልጿል።
አሜሪካ በኢራን ላይ ለምትፈጽማቸው ጥቃቶች ኢራን በዮርዳኖስ፣ በኩዌት እና በባህሬን ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች እና ወታደራዊ ተቋማት ላይ የአጸፋ እርምጃ እየወሰደች ነው።



















