ኢራን በሚያዚያ ወር ከአሜሪካ ጋር የተኩስ አቁም ከደረሰች ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ ወደ እስራኤል ሚሳዔሎችን አስወነጨፈች። የእስራኤል ጦር የቴህራን ጥቃትን ተከትሎ በምዕራብ እና ማዕከላዊ ኢራን በሚገኙ ወታደራዊ ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ሚሳዔሎቹ “ለሳምንት የሚቀጥለው ጥቃት” የመጀመሪያ ነው ሲል አስታውቋል።
የእስራኤል ጦር በቴሌግራም ገጹ ላይ "ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የእስራኤል አየር ኃይል የኢራን አሸባሪ አገዛዝ ንብረት የሆኑ በምዕራብ እና ማዕከላዊ ኢራን የሚገኙ ወታደራዊ ዒላማዎችን ደብድቧል" ሲል ጽፏል።
እስራኤል በበኩሏ በሰሜናዊ እስራኤል ሚሳዔሎችን ማክሸፏን ገለጻ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ ግን ያለችው የለም።
እሁድ ዕለት እስራአል በደቡባዊ ቤይሩት የሄዝቦላህ ዒላማዎች ላይ ድብደባ መፈጸሟን አስታውቃለች።
የጦሩ ቃል አቀባይ ኢራን “ትልቅ ስህተት ሰርታለቸ” ሲሉ ተናግረዋል።
ፎክስ ኒውስ በበኩሉ ትራምፕ ኢራንን “ይበቃል ወደ ድርድር ጠረጴዛው ተመለሽ” ሲሉ መናገራቸውን ዘግቧል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለአክሲዮስ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ለኢራን ሚሳዔሎች የአጸፋ ምላሽ እንዳይሰጡ እንደሚናግሯቸው ገልጸዋል።
“አሁን ለቢቢ እደውልለታለሁ እና የአጸፋ ምላሸ እንዳሰጥ እነግረዋለሁ” ብለዋል።
“ሁለቱም የራሳቸው ደስታን አግኝተዋል። እስራኤል አጥቅታለች እናም ኢራን አጥቅታለች። ተጨማሪ አንፈልግም።”
“ከኢራን ጋር ወደ መጨረሻው ስምምነት ተቃርበናል። ጥሩ ስምምነት ነው የሚሆነው። አሁን እየሆነው ባለው የተነሳ ይህንን ማጣት አልፈልግም” ማለታቸውን አክሲዮስ ዘግቧል።
ትራምፕ አክለውም እስራኤል ዳግም ጥቃት ከፈጸመች ግጭቱ “ለ47 ዓመታት ወይም እንደ 3000 ዓመታቱ” ይቀጥላል ብለዋል።
አክሲዮስ ትራምፕ ለኔታንያሁ መደወላቸውን ጨምሮ ዘግቧል።
የእስራኤል ጦር በበኩሉ በቴሌግራም ገጹ ላይ ሌተናል ጄነራል ኢያል ዛሚርን በመጥቀስ “ጠላትን በቁርጠኝነት ትዕዛዝ እንደተሰጠን መደብደብ አንጀምራለን” ብሏል።