ትራምፕ፣ ኔታንያሁ ስምምነቱን ከመቀበል ውጭ አማራጭ የለውም አሉ

የፎቶው ባለመብት, Kevin Dietsch via Getty Images
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉትን ማንኛውም ስምምነት ኔታንያሁ ከመቀበል ውጭ አማራጭ የላቸውም ሲሉ ለፋይናንሻል ታይምስ ተናገሩ።
ትራምፕ ለፋይናንሻል ታይምስ “አማራጭ የለውም” ሲሉ በስልክ ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ወቅት ተናግረዋል። “እኔ ነኝ ውሳኔውን የምሰጠው። እኔ ነኝ ሁሉንም ውሳኔ የምሰጠው። እርሱ [ኔታንያሁ] አይደለም ውሳኔ ሰጪው” ብለዋል።
ትራምፕ ከአክሲዮስ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ወቅት ኔታንያሁ የሰላም ስምምነቱ እንዳይከሽፍ ለማድረግ ለኢራን ጥቃት የአጸፋ ምላሽ እንዳይሰጡ እንደሚነግሯቸው ገልጸው ነበር።
ትራምፕ ከፋይናንሻል ታይምስ ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ላይ ደግሞ የተፈጸመው ጥቃት “በስምምነቱ ላይ ምንም ተጽዕኖ አይኖረውም” ብለዋል።
አክለውም “እንዴት ሆኖ እንደሚጠናቀቅ እናያለን። ላለፉት 3000 ዓመታት 47 ዓመታት ሲሆን የነበረው ነገር ነው፤ ወይም እንደምትቆጥርበት መንገድ ይወሰናል” ብለዋል።

