ቀጥታ, ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነትን ለማረም ፍላጎት እንዳላቸው ተነገረ

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሦት ወራት በፊት የተጀመረውን የአሜሪካ እና ኢራን ጦርነት ለመቋጨት የሚያስችለውን ስምምነት ለማስተካከል ፍላጎት እንዳላቸው የዋሽንግተን መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።

ጭምቅ ሃሳብ

ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነትን ለማረም ፍላጎት እንዳላቸው ተነገረ

የቀጥታ ሽፋን

  1. ሩሲያ በዩክሬን ከተሞች በፈጸመችው ጥቃት ቢያንስ ዘጠኝ ሰዎች ተገደሉ

    ሞስኮ የፈጸመችው ጥቃት በነዳጅ ማደያ እሳት አቀጣጥሏል።

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    ሩሲያ በዩክሬን ዋና ዋና ከተሞች ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ ዘጠኝ ሰዎች እንደተገደሉ እና ብዙዎች እንደቆሰሉ ተገለጸ።

    በዲፕሮ ከተማ አምስት ሰዎች ሲገደሉ 25 ሰዎች ተጎድተዋል። ዛሬ ንጋት ላይ በደረሱ ጥቃቶች በመዲናዋ ኪቭ አራት ሰዎች መገደላቸው እና 51 መቁሰላቸውም ተዘግቧል፤ 35 ያህሉ ደግሞ ሆስፒታል ገብተዋል።

    የኪቭ ከንቲባ ቪታሊ ክሊሽኮ እንዳሉት ሁለት ግዙፍ የመኖሪያ ሕንጻዎች የተመቱ ሲሆን፤ ሰዎች በፍርስራሽ ሥር ተቀብረው ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።

    ዩክሬን ባለፈው ወር የድሮን ድብደባ በመፈጸሟ በምላሹ “ስልታዊ ጥቃት” ለማድረስ ሞስኮ ስትዝት ቆይታለች።

    ሩሲያ በቁጥጥሯ ሥር ባዋለችው የዩክሬን ሉሀንስክ ግዛት በደረሰው የድሮን ጥቃት 21 ሰዎች ተገድለዋል።

    የኪቭ ከንቲባ ነዋሪዎች ከቤታቸው እንዳይወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል። “ጠላታችን በባለስቲክ ሚሳዔል ጥቃት እየፈጸመ ነው” ሲሉም ተናግረዋል።

    በአብዛኞቹ የዩክሬን ከተሞች የአየር ጥቃት ማስጠንቀቂያ ደወሎች እየተሰሙ ነው። በማዕከላዊ ኪቭ ጭስ መታየቱም ተገልጿል።

    በሌላ በኩል በሩሲያ ኢልስኪ የነዳጅ ማቀነባበሪያ የደረሰ ጥቃት እሳት ማስነሳቱ ተገልጿል።

    ኪቭ ውስጥ የበርካታ ድሮኖች እና ፍንዳታ ድምጽ እየተሰማ ይገኛል። ሞስኮ የፈጸመችው ጥቃት በነዳጅ ማደያ እሳት አቀጣጥሏል።

    ጥቃት የደረሰበት ሕንጻ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

  2. ሄዝቦላህ በእስራኤል ላይ ጥቃት ማድረሱን ለማቆም መስማማቱን ሊባኖስ ገለጸች

    ቤሩት

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    ሄዝቦላህ በእስራኤል ላይ ጥቃት ማድረስ እንዲያቆም ከአሜሪካ የቀረበለትን ሐሳብ መቀበሉን ሊባኖስ አስታወቀች።

    እስራኤልም በሊባኖስ መዲና ቤሩት ጥቃት ላለመፈጸም መስማማቷም ተገልጿል።

    አሜሪካ የሚገኘው የሊባኖስ ኤምባሲ “አሜሪካ ሁለቱም ወገኖች ጥቃት እንዳያደርሱ ያቀረበችውን ምክረ ሐሳብ ሄዝቦላህ ተቀብሏል” ብሏል።

    የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁም ስምምነት ላይ መደረሱን አረጋግጠዋል።

    ሆኖም “ሄዝቦላህ ከተሞቻችን እና ዜጎቻችን ላይ ጥቃት ከፈጸመ ግን ቤሩትን እንደበድባለን” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

    የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኔታንያሁ እና ከሄዝቦላህ ተወካዮች ጋር መወያየታቸውን ጠቅሰው “ተኩስ ለማቆም ተስማምተዋል” ብለዋል።

    እስራኤል በሊባኖስ የምታደርሰው ጥቃት የኢራን እና አሜሪካን የተኩስ አቁም ስጋት ውስጥ እንደሚጥል ቴህራን መግለጿ ይታወሳል።

    የሊባኖስ ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ “ሄዝቦላህ እስራኤል ላይ ጥቃት ካልፈጸመ እስራኤልም በቤሩት ጥቃት እንደማታደርስ ተስማምተናል” ብሏል።

    የተኩስ አቁሙ በሒደት “ሌሎች የሊባኖስ አካባቢዎችን እንደሚሸፍን” ተገልጿል።

    ኔታንያሁ በበኩላቸው “የእስራኤል መከላከያ ኃይል በታቀደው መሠረት በደቡብ ሊባኖስ ዘመቻውን ይቀጥላል” ብለዋል።

    ሁለቱ ወገኖች ተኩስ ለማቆም መስማማታቸውን ትራምፕ ከገለጹ በኋላ የተወሰኑ ግጭቶች መነሳታቸው ተዘግቧል።

  3. ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነትን ለማረም ፍላጎት እንዳላቸው ተነገረ

    ትራምፕ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሦት ወራት በፊት የተጀመረውን የአሜሪካ እና ኢራን ጦርነት ለመቋጨት የሚያስችለውን ስምምነት ለማስተካከል ፍላጎት እንዳላቸው የዋሽንግተን መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።

    ለውጦቹ በሆርሙዝ ወሽመጥ እና የተብላላ የዩራኒየም አወጋገድ ጋር የተያያዙ እንደሆኑ በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ኒውስ ዘግቧል።

    ዋይት ሐውስ አስተያየት እንዲሰጥ ቢጠየቅም ምላሽ አልሰጠም።

    የኢራን ዋና ተደራዳሪ መሐመድ ባገር ጋሊባፍ እሑድ ዕለት የኢራን መብት ሙሉ ለሙሉ እስካልተጠበቀ ድረስ ቴህራን ምንም ዓይነት ስምምነት አትፈጽምም ብለዋል።

    የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለማራዘም በሚያስችለው ማዕቀፍ ላይ ፕሬዝዳንት ትራምፕ እና ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር አርብ ዕለት ለንግግር ቢቀመጡም፤ ስብሰባው ቀጣይ እርምጃዎች ላይ ግልፅነት ሳይኖረው ተጠናቋል። ሙሉውን እዚህ ያንብቡ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነትን ለማረም ፍላጎት እንዳላቸው ተነገረ